Seattle Public Schools

ስለ በደንብ የተደራጁ ትምህርት ቤቶች አስመልክቶ ወቅታዊ መረጃ 

Summary: የትምህርት ስርዓታችንን ትክክለኛ መጠን ለማድረግ እርምጃዎችን እየወሰድኩ ለ2025-26 የትምህርት ዘመን የበጀት ጉድለትን ለመፍታት የሚረዳ የተሻሻለ እቅድ አዘጋጅቻለሁ።በዚህ ክለሳ መሰረት፣

ስለ በደንብ የተደራጁ ትምህርት ቤቶች አስመልክቶ ወቅታዊ መረጃ 

ውድ የሲያትል የህዝብ ትምህርት ቤቶች ቤተሰቦች፣ሰራተኞች እና ማህበረሰብ፣ 

በደንብ ስለተደራጁ የትምህርት ቤቶች ስርዓት ለመዘርጋት ስናቅድ ሀሳብዎን ለመግለፅ ጊዜ ስለወሰዱ እናመሰግናለን። ድምፅዎን ሰምተናል፣አሁን ስለ እቅዱ ያለዎትን ብዙ ትክክለኛ ስጋቶች ተረድቻለሁ። 

ይህን የመሰለ መጠነ ሰፊ ለውጥ ለማሳደግ የተማሪዎቻችን፣ቤተሰቦቻችን እና የሰራተኞቻችን ድጋፍ እንደሚያስፈልገን እናውቃለን።ተስፋዬ የትምህርት ቤቶቻችንን ማህበረሰቦች በሚያስከብር መንገድ ወደፊት እንድንራመድ የሚያስችለንን የመተማመን ደረጃ እንደገና ለመመስረት አብረን እንድንሰራ ነው። 

በአስተያየትዎ ላይ ለማሰላሰል የተወሰነ ጊዜ ከወሰድኩ በኋላ፣የትምህርት ስርዓታችንን ትክክለኛ መጠን ለማድረግ እርምጃዎችን እየወሰድኩ ለ2025-26 የትምህርት ዘመን የበጀት ጉድለትን ለመፍታት የሚረዳ የተሻሻለ እቅድ አዘጋጅቻለሁ።በዚህ ክለሳ መሰረት፣ለ2025-26 የትምህርት ዘመን አምስት ትምህርት ቤቶችን ለማዋሃድ ሀሳብ አቀርባለሁ።ከዚህ የመጀመሪያ የትምህርት ቤቶች ማዋሀድ የምንማረው ነገር የወደፊት ተግባራችንን ይመራናል። 

እንዲሁም ቤተሰቦቻችን በዲስትሪክታችን ውስጥ ያሉትን አብዛኛዎቹን አቅርቦቶች ከፍ አድርገው እንደሚመለከቱ ግልጽ ነው።በተሻሻለው እቅድ፣K-8 እና አማራጭ ትምህርት ቤቶችእንደ መስማት የተሳናቸው እና የመስማት ችግር ያለባቸው እና የባለሁለት ቋንቋ ፕሮግራሞች(Dual Language Immersion) ያሉ ልዩ የአገልግሎት ሞዴሎችን ጨምሮ -ለመጪው የትምህርት ዘመን ግምት ውስጥ አይገቡም። 

ሲያትል የሕዝብ ትምህርት ቤቶች፣ልክ እንደሌሎች ዲስትሪክቶች፣የተማሪዎች ምዝገባ ማሽቆልቆል እና በጣም እውነተኛ የበጀት እጥረት እያጋጠመው ነው።ይህ አዲስ አካሄድ በሚቀጥሉት አመታት የበጀት ሚዛንን በመጠበቅ መቆራረጥን ለመቀነስ ያለመ ነው።ለ2025-26 የትምህርት ዘመን ወደ 100 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የበጀት ጉድለትን ለመዝጋት ጠንክረን እየሰራን ነው።እያንዳንዱ የትምህርት ቤቶች ማዋሃድ ይህንን ጉድለት በመጠኑ ይቀንሳል እንዲሁም የረጅም ጊዜ የፋይናንስ መረጋጋት አስተዋፅዖ ያደርጋል። 

የትምህርት ቤቶች ማዋሃድ የምርጫ መስፈርቶች

በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት፣በደንብ የተደራጁ የትምህርት ቤቶች ቡድን እና እኔ በ2025-26 የትምህርት ዘመን ለማዋሀድ የታሰቡትን አምስት ትምህርት ቤቶች እንወስናለን።የሶስተኛ ወገን ኤክስፐርት ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የግምገማ ሂደቱን ያረጋግጣል።

የምርጫው ሂደት በሚከተሉት መስፈርቶች ላይ የተመሰረተ ነው: 

  • የህንፃው ሁኔታ:የግንባታው ደህንነት እና የጤና ደረጃዎች
  • የመማሪያ አካባቢ:ሁሉንም የትምህርት ዓይነቶች ለመደገፍ የፋሲሊቲ ዲዛይን
  • ምዝገባን እና አቅምን መተንተን:ተቋሙ 400+ ተማሪዎችን የመያዝ አቅሙ፣ለጠንካራ የIEP አገልግሎቶች እና የቅድመ መደበኛ ትምህርት መማሪያ የሚሆኑ  ክፍሎችን ጨምሮ
  • የተማሪዎች እና የሰራተኞች መቆራረጥን መቀነስ:በተቋሙ ውስጥ በተቻለ መጠን ብዙ ተማሪዎችን እና ቤተሰቦችን በአንድ ላይ የማቆየት ችሎታ
  • የተማሪዎችን የልዩ የአገልግሎት ሞዴሎች ተደራሽነት መጠበቅ፡ተቋሙ ተማሪዎች እንዲበለጽጉ የሚፈልጓቸውን ግብዓቶች የማስቀመጥ ችሎታ

ቀጥሎ ምን ይሆናል

በጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ የመጀመሪያ ምክሮችን ለቦርዱ እናካፍላለን ብለን እንጠብቃለን። 

ይህን አስፈላጊ ውሳኔ አብረን በምንመራበት ጊዜ እንዲሳተፉ እና ሃሳብዎን እንዲያካፍሉ እናበረታታዎታለን።ለሁለቱም አጠቃላይ መረጃ ለመስጠት እንዲሁም ልዩ ዕቅዶች እና ተጽዕኖ ለሚደረሰባቸው ትምህርት ቤቶች የሽግግር ድጋፎችን ለማካፈል የማህበረሰብ ስብሰባዎችን እናካሂዳለን። 

እያዳመጥን ነው፣ እና የእርስዎን አስተያየት እናከብራለን – ለተማሪዎቻችን ጠንካራ የወደፊት ሁኔታን ለመፍጠር ወሳኝ ነው። 

እባክዎን ጥያቄዎችዎን ወይም ግብረ መልስዎን በ Let’s Talk form በኩል ያስገቡ )።ለበለጠ መረጃ፣ወደ በደንብ የተደራጁ ትምህርት ቤቶች  ድረ ገፅይሂዱ።

ስለ ትምህርት ቤቶቻችን የወደፊት ሁኔታ በጥልቅ ስለምታስቡ እና ለቀጣይ ድጋፍዎ እናመሰግናለን።

ከሰላምታ ጋር፣

Dr. Brent Jones
ዋና ሃላፊ
ሲያትል የሕዝብ ትምህርት ቤቶች